ከኢትዮጵያ የንግድ ልዑካን ጋር ወደ አውስትራሊያ ተጉዘው የነበሩት የኢትዮጵያ ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አውስትራሊያ ከሄዱ በኋላ ሪፖርት ሳያደርጉ አንድ ወር ማስቆጠራቸው ጥያቄ አስነሳ፡፡ በዚህም ምክንያት ቼክ ላይ የሚፈርም በመጥፋቱ ችግር መፈጠሩን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በቅርቡ በተካሄደ አወዛጋቢ ምርጫ የኢትዮጵያ የዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት አቶ ኢያሱ ሞሲሳ፣ በአንድ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣን ከተመራ የልዑካን ቡድን ጋር ዘርፍ ምክር ቤቱን በመወከል ወደ አውስትራሊያ ከተጓዙ በኋላ፣ ሌሎች የልዑካን ቡድን አባላት ሲመለሱ እርሳቸው መቅረታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
እንደ ምንጮች ገለጻ ከሆነ አቶ ኢያሱ መመለስ የነበረባቸው ከሦስት ሳምንታት በፊት ነበር፡፡ የጉዞ ፕሮግራሙ ካለቀ በኋላ ሪፖርት ሳያደርጉ በመቆየታቸው፣ በዚያው ቀርተዋል የሚል ድምዳሜ ላይ ተደርሷል፡፡ በተለይ ከተረከቡት ኃላፊነት አንፃር ውክልና ሳይሰጡ አንድ ወር መቆየታቸው የጽሕፈት ቤቱን እንቅስቃሴ እንዳስተጓጎለ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ Continue reading →