ቀን ፡ – 12/07/2012 ዓ. ም
Ref No. /ቁጥር ፡ – 59/03/20
ለክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ፡
የኢ.ፈ.ዲ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስቴር እና የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ፡
አዲስ አበባ፡
ጉዳዩ፦ በዋናነት በምዕራብ እና ደቡብ ኦሮሚያ አከባቢዎቸ ስላለው የሰብዓዊ መብቶች
አያያዝን ይመለከታል።
ክቡር ጠ/ሚኒስትር፤
በመጀመሪያ በሃላፍነት በሚመራው የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብቶች ሊግ (The Human Rights
League of the Horn of Africa- HRLHA) ድርጅት ሥም የከበረ ሠላምምታዬ ይድረስዎ።
ይህንን ዴብዳቤ ልፅፍልዎ የወደድኩት በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ በአጠቃላይ በተለይ ደግሞ
በምዕራብ እና በደቡብ ኦሮሚያ ዞኖች ውስጥ ስለሚታየዉ የሰቢአዊ መብቶች አያያዝ አሳሳብነት
መሰረት በማድረግ ነው።
ክቡር ጠ/ሚኒስትር፤
ክቡርነትዎ እንደምገነዘቡት፤ የኢትዮጵያ ህዝቦች እና ብሔር ብሐረሰቦች ለአመታት ባደረጉት እልህ
አስጨራሽ ትግሎች በሀገሪቱ ወስጥ ለዘመናት ተንሰራፍቶ የቆየዉን ኢ-ሰብዓዊነት እና ኢዲሞክራሳዊ የሰፈነበትን ሥርዓቶችን በማስወገድ ለዉጦቸን አስመዝግበዋል፡፡
ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ኢትዮጵያን ስመራ የነበረው የኢህአዲግ መንግሥት ከፍተኛ
የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና በደል ስፈፅም የነበረዉን ከባድ መስዋዕት ከፍሎ ማስወገዱ ከማንም
የተደበቀ አይደለም። የኢህአዲግ የግፍ አገዛዝ ያንገሸገሸው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጫፍ እስከ ጫፍ
መብቱ እና ሉዓላዊነቱ እንድከበርለት ከፍተኛ ተጋድሎ አድርጓል። በተለይ ከ2006 ዓ.ም ወዲህ
የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብቶች ሊግ Continue reading