” Gaafa Xiiqii Gooti Hin Ciisu” Hawwisoo Qeerroo Bilisummaa Irraa Wallee Warraaqsaa
Aside
SEENAA Y.G(2005)
Filannoo fi waggaa 40ffaa TPLF wal qabsiisanii , addatti hiwaatoonni waan isaan hololaa jiran kan qalbifateef, Bilisummaa keenya goonfachuuf maaltu akka nu irraa eegamu tilmaamu hin dadhabu. Ummati qabsoo gaggeessu tokko,sochii isaa guyyu akkuma hordofu, sochii diinaas hordofuun dirqama. Qabsoon Ummata Oromoo Biyya keessaa fi alatti gama hundaan gaggeeffamaa jiru, jabiina horachaa jiraachuun beekamaadha. Kun diinaaf tasgabbii kan kennu miti. akka walii galaatti, sochii amma taasifamaa jiru caalaatti jabeessuu fi tarkaanfii diina mogolee cabsun deeggaramu qofatu nu hafa yoon jedhe dhugaa irraa fagaachuu hin ta’u. Sochii Ilamaan Oromoo gama hundaan taasisan tarkaanfii diina irratti fudhatu daran jabeessinee itti fufu fi hegaree diinaa yaaddoo keessa galchuu hanqachuu keenyatu, diina Oromoo kan ta’ee wayyaanee fi jala deemtoonni isaanii akka arraba dheeratan taasisaa jira.
ከሰሞኑ አቶ አባይ ፀሃዬ አዲሱን የፊንፊኔ ማስተር ፕላን አስመልክተው የተናገሩት የዛቻና የፉከራ ቃል መላውን የኦሮሞ ህዝብ ያስቆጣና ምናልባትም አዲሱ የማስተር ፕላን ፕሮግራም በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ፍፁም ተቀባይነት የሌለው እና ከባድ መስዋትነት የተከፈለበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የአቶ አባይ ፀሃዬ “ልክ ይገባሉ” የሚለው ያረጀና ጊዜው ያለፈበት የፉከራ ቃል የኦሮሞን ህዝብ በበለጠ ለነፃነቱ የሚያደርገውን ትግል አጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያነሳሳ ንቀት የተሞላበት ንግግር ነው::
እንዲህ ያለው ዛቻና ማስፈራሪያ ለዘመናት የተጨቆነንና የነፃነት ጥያቄን አንግቦ የተነሳን ሰፊ ህዝብ በይበልጥ እንዲጠናከርና የተፈረደበትን የልክ ይገባል ዛቻ አፀፋዊ ምላሽ ለመስጠት እራሱን ዝግጁ እንዲያደርግ የሚጋብዝ ባለንበት ዘመን ሊሰነዘር የማይገባ አፀያፊ ቃል ነው:: ተናጋሪው የወቅቱ ባለስልጣን በተለይ በኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳድር በየደረጃው የሚገኙ ባለስልጣናትን ለአዲሱ የፊንፊኔ ማስተር ፕላን ፕሮግራም ተፈፃሚነት ግንባር ቀደም እንቅፋቶች መሆናቸውን ንቀት በተሞላበት መልኩ ከተናገሩ በኋላ እንደርሳቸው “የልክ ይገባል” ፉከራ ከሆነ እነዚህ በማስተር ፕላኑ ላይ ተቃውሞ ያላቸውና እንቅፋት የሆኑ በየደረጃው ያሉ የክልሉ ሰራተኞች የመጀመሪያ ልክ የሚገቡ ሰዎች ይሆናሉ::
ከኚሁ የዘመናችን ባለስልጣን የማስፈራሪያ ንግግር አንድ ልብ ብለን መገንዘብ ያለብን ነገር ያለ ይመስለኛል ይሔውም ለልማት ሳይሆን ለጥፋት ቆርጠው የተነሱ የህወሃት አባላት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስ በከፍተኛ ስልጣን ከሚገኙ የክልሉ ተወላጆች እስከ ወረዳ ቀበሌ በሚገኙ የኦሮሞ ተወላጆች ያልጠበቁትን ከፍተኛ ተቃውሞ የተመለከቱበት ወቅት ከመሆኑ አንፃር ምናልባት ቀድሞ የታየው ተቃውሞ መልኩን ቀይሮ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል ይችላል የሚል ስጋት ስለሚፈጠር እንደ አማራጭ ሊጠቀሙ የሚችሉበት ነገር በግለሰብም ደረጃ ሆነ ባጠቃላይ እንደ ህዝብ የማስፈራሪያና የማሸማቀቂያ ቃላትን በመወርወር ከወዲሁ የተቃውሞ ድምፆችን ለማቀጨጭ መሞከር ነው:: አቶ አባይ ፀሃዬ የፈፀሙትም ይሄንኑ ይመስለኛል::
ያለንበት ዘመን አንዱ ሌላውን ልክ እያስገባ የሚኖርበት ዘመን አይደለም:: ይልቁኑ የመብት ጥያቄ ለሚያነሳ ህዝብ ተገቢውን መልስ በመስጠት በሃገሪቱ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠርና የህዝቦች መብት በእኩል አይን ሊከበር የሚችልበትን መንገድ መቀየስ እንጂ:: አቶ አባይ ፀሃዬ ይህ የገባቸው አይመስሉም:: ለ24 ዓመታት በህዝብ ጫንቃ ላይ ቁጭ ብሎ ህዝብን በንቀት አይን ሲመለከቱበት የነበረ ጊዜ አሁን ያበቃለት መሆኑን መረዳት ይኖርባቸዋል:: ብሶት ህውሃትን ብቻ ሳይሆን ሌላውንም የማይወልድበት ምክንያት ሊኖር አይችልምና::