Daily Archives: July 21, 2018
Hiriira guyya kaleessaa “Hiriira Lamiin Lammiif” irratti yaada ummataa.
Aside
SAGALEE QEERROO:ADOOLESSA 20, 2018
Aside
የኢትዮጵያ መንግስት በኦሮሞ ህዝብ ላይ አላስፈላጊ ጦርነት ከማካሄድ መቆጠብ አለበት።
Aside
(የኦነግ መግለጫ ሓምሌ 20 ቀን 2018ዓም)
(የኦሮሞ ነጻነት ድምጽ/VOL – ሓምሌ 20, 2018) ከኢህኣደግ ውስጥ የተገኘ ተጨባጭ መረጃ እንደሚያመለክተው የኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳና አስተዳደሩ በኦነግና በኦሮሞ ህዝብ የነጻነት ትግል ላይ ሲያካሂዱት ከነበረውና በማካሄድ ላይ ከሚገኙት ጦርነት እየቆሙ አይደሉም። አቶ ለማ መገርሳ፣ አቶ አባዱላ ገመዳ፣ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላና ሌሎች ሰዎችም የሚገኙበት አንድ ቡድን የዚህ ጦርነት ጉዳይ በግንባር ቀደምነት እየገፉት እንዳሉም ለመረዳት ተችሏል። ይህ ቡድን ከኦነግ ጋር የተጀመረው የሰላም ድርድር በእንጥልጥል ቆይቶ ቢያንስ ለአንድ ወር በኦነሰ ላይ የሚካሄደው ዘመቻ እንዲቀጥል በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር. ዐብይ አህመድ ላይ ግፊት በማድረግ ማሳመኑምት ተሰምቷል።