በኦሮሚያ የህዝባዊ አብዮት ጥሪ ወረቀቶች መበተናቸው ቀጥሉአል

በኢትዮጵያ ላይ የተጫነው ግፈኛና ዘረኛ አገዛዝ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከኢትዮጵያዊያን ትከሻ ላይ ተሽቀንጥሮ ይውድቅ ዘንድ ግፊቱና ህዝብንም ለዚሁ ትግል የማያነሳሳ ጥሪ መቅረቡ ተጡዋጡፎ እንደሚገኝ ተገልጹአል::

በአዲስ አበባና በሌሎች የኦሮሚያ ዋና ከተሞች የተበተኑ ጥሪ ወረቀቶች ህዝብ ለነጻነቱ ሲል ወያኔ እያደረሰ ያለውን የጥፋት ተልዕኮ ለማስቆም ሆ ብሎ መነሳት ያለበት ጊዜው አሁን መሆኑን የሚያመለክት ነው ተብሎአል።

ከተበተኑት ጽሁፎች ውስጥ አባይ ወንዝን በላያችን ላይ ያለውን የአምባገነንነት ቀምበር ካስወገድን በሁአላ እንሰራዋለን የሚል እንደሚገኝበት ተገልጹአል::

ከበርካታ ቀናት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተለያዩ ቀስቃሽ ወረቀቶች በየግድግዳው እንደሚለጠፉና ሲበተኑም እንደነበር በተደጋጋሚ የተዘገበ ሲሆን ሰሞኑን ደግሞ በቃ የሚሉ ጽሁፎ በየመንገዱ ተበትነው እንደሚገኙ ተገልጹአል::

ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ በተለይም የሰሜን አፍሪቃው ህዝባዊ አብዮት ከተቀሰቀሰ ወዲህ በሃገር ውስጥ ያለው እንቅስቃሴ እጂግ እያስፈራውና እያስጨነቀው እንደመጣ ሲዘገብ ከዚህ ጭንቀት መውጫ መንገድ አድርጎ እየወሰደ ያለው ርምጃም ንጹሃን ዜጎችን በጂምላ ወደ እስር ቤት ማጎር እንደሆነ በርካታ የዜና አውታሮች የዘገቡት መሆኑ ይታወቃል::

ባለፈው አንድ ወር ውስጥ የመለስ ዜናዊ ዘረኛ አገዛዝ በጅምላ ካሰራቸው እና ለጊዜው ቁጥራቸው ከታወቁት 200 በላይ የኦሮሞ እስረኞች ውስጥ አንድ መቶ ሃያ አንዶቹ በሽብርተኝነት ክስ ሊመሰረትባቸው እንደሆነ መለስ ዜናዊ መጋቢት 27 በራሱ አምሳል ጠፍጥፎ ለሰራው ፓርላማ ተብዬ ሸንጎ ንግግር ባደረገበት ወቅት በሰላማዊ ትግል የፖለቲካ አላማቸውን እውን ማድረግ እንችላለን ብለው በይፋ የሚንቀሳቀሱትን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለማስፈራራት በግፍ የታሰሩት አባላቶቻቸው ሽብር ለማካሄድ የሚንቀሳቀሱ ናቸው በማለት እንደወነጀላቸው ይታወቃል።

በራሪ ወረቀት በከተማ ውስጥ የመበተኑ ሥራ ተፋፉሞ በመቀጠል ሰሞኑን በአዲስ አበባ፤ በአዋሳ፤ በኮምቦልቻ፤ በአርባምንጭ፤ በደሴ፤ በድሬደዋ እና ሌሎች ከተሞች እየተበተነ እንደሆነ ለማረጋገጥ ተችሎአል።ከስድስት ኪሎ ወደ ጊዮርጊስ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የሃብተ ጊዮርጊስ ድልድይ (አፍንጮ በር ድልድይ) ላይ ሞት ለወያኔ የሚል ጽሁፍ በትላልቅ ፊደላት ተጽፈው እንደነበር ይታወሳል ፣፡

የወያኔ አገዛዝ ፍርሃቱ ከቁጥጥሩ ውጭ እየወጣ ነው

የወያኔ አገዛዝ በአዲስ አበባና በዋና ዋና የክልል ከተሞች የደህንነትና የጸጥታ ጉዳይ አሳሳቢነትን አስመልክቶ ሕዝባዊ ስብሰባ መደረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ የዘረኛው አምባገነን አገዛዝ ባለስልጣናትና ሆድ አደሮች ኢትዮጵያ ውስጥ ወጣቶች የሚመሩት ሕዝባዊ ንቅናቄ እንዳይከሰት ሰግተዋል ፡፡

የደህንነትና የጸጥታ ጉዳይ አሳሳቢነትን አስመልክቶ የተካሂደው ሕዝባዊ ስብሰባ የወጣት ማህበራትን፣ የሴቶች ሊግን፣ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችንና የመንግሥት ሠራተኞችን ለይቶ የጠራ ሲሆን የዘረኛው አገዛዝ ከፍተኛ አመራሮች ስብሰባውን ስብሰባዎቹን መምራታቸው ተገልጹአል::

የስብሰባው አጀንዳዎች የአካባቢና የሀገር ልማት ቁርኝት፣ የሀገርን ልማት የሚያደናቅፉ የደህንነትና የጸጥታ ጉዳዮች፣ ለወጣቶች የብድር መስፈርትና አቅርቦት፣ ወቅታዊ የዓለም ሁኔታና የኢትዮጵያ አጠቃላይ ዕድገት የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ይገኙበታል በማለት ምንጮቻችን ገልጹአል፡፡

በስብሰባው ላይ የተሳተፉት ወጣቶች ከንቁ የኢህአዴግ ፓርቲ አባላትና ካድሬዎች ጋር በአንድነት በመጠርነፍ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ በአካባቢ ልማትና የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ተጠሪ ሆነው እንዲንቀሳቀሱና እንዲሰሩ እየተደረገ ሲሆን ይህም በምሥራቅ አፍሪካና በመካከለኛው ምሥራቅ የዓረብ አገራት ላይ የተከሰተውን ዓይነት ሕዝባዊ መነቃቃት በኢትዮጵያም እንዳይከሰት ለመከላከል ያስችላሉ ከተባሉ ልዩ ልዩ ስትራቴጂዎች ውስጥ አንዱ ነው።

ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ በተለይም የሰሜን አፍሪቃው ህዝባዊ አብዮት ከተቀሰቀሰ ወዲህ በሃገር ውስጥ ያለው እንቅስቃሴ እጂግ እያስፈራውና እያስጨነቀው እንደመጣ ሲዘገብ ከዚህ ጭንቀት መውጫ መንገድ አድርጎ እየወሰደ ያለው ርምጃም ንጹሃን ዜጎችን በጂምላ ወደ እስር ቤት ማጎር እንደሆነ በርካታ የዜና አውታሮች የዘገቡት መሆኑ ይታወቃል::

ከስድስት ኪሎ ወደ ጊዮርጊስ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የሃብተ ጊዮርጊስ ድልድይ (አፍንጮ በር ድልድይ) ላይ ሞት ለወያኔ የሚል ጽሁፍ በትላልቅ ፊደላት ተጽፈው ነበር ፣፡ በራሪ ወረቀት በከተማ ውስጥ የመበተኑ ሥራ ተፋፉሞ በመቀጠል ሰሞኑን በመርካቶ ውስጥ እየተበተነ እንደሆነ ለማረጋገጥ ተችሎአል።

በመላ አዲስ አበባ የደህንነት እና የጸጥታ ጉዳይ ስብሰባ ተደረገ

(Qeerroo News, Finfinnee, April 17, 2011) ኢህአዴግ በመላ አዲስ አበባ የደህንነት እና የጸጥታ ጉዳይ ላይ የሚያተኩር ስብሰባ  አደረገ፤ ልዩ ልዩ የሰላምና የልማት ኮሚቴዎችንም በአዲስ መልክ አዋቅሯል፡፡

በሕዝባዊ ውይይቱ ላይ ከፌዴራል ፖሊስ የተወከሉ ባለሥልጣናት በአሥሩም ክፍለ ከተሞች በመገኘት ወላጆች ልጆቻቸውን ተገቢ ባልሆኑ ቦታዎችና እንቅስቃሴዎች ላይ እንዳይሳተፉ እንዲቆጣጠሩ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

በአዲስ አበባ አሥሩም ክፍለ ከተሞች አዳራሾች ባካሄደው ሕዝባዊ ስብሰባዎች ላይ የኢህአዴግ አመራር አባላት የተገኙ ሲሆን ከወጣት ማህበራት፣ ከሴቶች ሊግ፣ ከጎበዝ ተማሪዎች፣ የመንግሥት ሠራተኞች እና ተደማጭ የአካባቢ ሰዎችንና ሽማግሌዎችን እንዲሁም የአካባቢው እድሮች አመራር አባላትን ያካተተ ልዩ ልዩ ከሚቴዎችን በአዲስ መልክ አቋቁሟል፡፡

በስብሰባው ላይ የኢህአዴግ አመራር አባላት የአምስት ዓመቱን የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድንና በቅርቡ መንግሥት ይፋ ያደረገውን የሚሊኒየም ግድብን በአምስት ዓመቱ ጊዜ ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆን ሕብረተሰቡ የቦንድ ግዢ በመፈጸም ተሳትፎ እንዲያደርግ ቀስቅሰዋል፡፡

ኢህአዴግ እሁድ ዕለት ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ በክልል ዋና ዋና ከተሞች ላይም መሰል ሕዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረጉን ምንጮቻችን ገልጸውልናል፡፡

በውይይቱ ላይ በደህንነት እና ጸጥታ ጉዳይ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢህአዴግ አመራር አባላት ማንኛውም ሥራ መሥራትን የሚፈልግ ሰው በአነስተኛና ጥቃቅን ቢደራጅ ብድር ሊያገኝ እንደሚችልና በግሌ እሰራለሁ ብሎ የተነሳሳ ሰውም ቢሆን የቀበሌ መታወቂያ ያለው ዋስ እስከ አቀረበ ድርስ ብድር ሊያገኝ እንደሚችልና በሂደት ደግሞ የሥራው አዋጭነትና ግለሰቡ ብድሩን የመመለሱ ሁኔታ እየታየ የብድር መጠኑ ሊጨምርለት እንደሚችል ገልጸዋል፡፡