መለስ እና ጋዳፊ

ከመላኩ ፀጋዬ መኮንን
በአንድ ሃገር ውስጥ ባለጌዎች እና ስድ አደጎች ስልጣን በጃቸው ሲገባ በምን መልክ አላግባብ እንደሚጠቀሙበት ብዙ ሩቅ ሳንባክን ከቀድሞው የዩጋንዳው ኢዲያሚን ዳዳ ዓንድ ብለን እስከ አቶ መለስ ዜናው አስረስ በየሃገራቱ የተፈጸሙትን ኢሰብአዊ ድርጊቶች ብንመለከትት ስለአምባገነኖች አገዛዝ ምንነት በቂ ማስረጃ ነው። በወዲ መለስ አገዛዝ በበረሃ ዘመናቸው አንስቶ የፈጸሙትናን ለከት ያጣ ርህራሄ የለሽ ተግባራቸው ይኽውና ለሃያ አመታት የያዝነው፤ ያየነው፤ የስቃይና የመከራ፤ የስደት፤ የሞት፤ የእስራት፤ የቸነፈርና የረሀብ እገዛዝ ዘክረውናል። አሁን ግን ይህ የሰቆቃ ኑሮ ወደዱም ጠሉም ለመጨረሻው ጊዜ መወገድ አለበት። የተቀመጡበት ወንበር ሲቆረቁረወት ካልተሰማወት ሊፈነግለወት ወስኞል ፤ውሳኔውን ባደባባይ እንዳይገልፅ ለጊዜው በብዙ ባላ ሊያስደግፉት እየሞከሩ ነው ይህ ሂደት አንቅሮ ከተፋወት ህዝብ ግፊት እስከመጨረሻው ሊደግፈወት አይችልም ፡፡ ለመደገፊያ ያውሸለሸሉት መሰላል ቀድሞ መበስበሱን ተረድተው እና ሕዝብ አንቅሮ የተፋወት መሆኑን አውቀው በጊዜ የመቋጠሪያ ውሉ ሳይጠፋ መሰስ ይበሉ፡፡

ሕዝቡ ከቀን አንድ ጀምሮ አንቅሮ ተፍቶወታል፤ እንደ እንሰሳ ሰው የተፋውን መልሶ አይውጥም አራት ነጥብ አይደል የሚሉት፡፡የማቆሚያ ነጥብ የሚያውቁ ስለሆነ ሕዝቡ ከአራት ነጥብ አልፎ ሃያ ነጥብ ብሏል። ታዲያ ሳልሞት አልወርድም የሚለውን የአምባ ገነኖች የሞኝ ዘፈን ትተው ሾለክ ቢሉ ለእርሰዎም ሆነ ለሀገሪቱ በጣም የተሻለ ነው።ለነገሩ የእርሰወ አይነት አገዛዝ የሚከተሉት ከራሳቸው ፍላጎት ውጭ ለሌላው ደንታ ቢስ መሆናቸውን አሁን በትኩሱ ጋዳፊ በልጆቹ ላይ ሳይቀር እልቂት እንዲፈጸምባቸው ያደረገ በመሆኑ ውሳኔወን በምን ላይ አንደሚያሳርፉ ለእርሰወ ልተወው፡ ግን ከታሪከው ሽርፍራፊ እንደምራዳው በሸር እንጂ በጀግንነት ወይም በሞገደኝነት ስለማይታሙ አራዳው የአስረስ ልጅ ቀኑን መዝኖ መሰስ ይላል የሚል ግምት አለኝ፡ ለማንኛውም ጊዜ ውሳኔ ይሰጣል፤ አሁን የተማመኑበት የዘር ጥርቅም ሲናድ በዚይን ጊዜ የእርሰወ ወኔ ይታያል፤ለነገሩ በቅርብ የሚያውቀወት ታጋዳሊ ሳይቀር በዋሉበት የጦር ግንባር ከድጋይ ስር ከመወተፍ ውጭ ቆምጨጭ ያለ ውሎ እንደማይሆንለወት ከግንባር አባሎቸወ የሚነገርለወ የታሪክ ባለድርሻ ነወት።

PDF article meles_ena_gaddafi

 

Leave a comment