“ልክ እናስገባቸዋለን” ጊዜ ያለፈበት የፉከራ ቃል

“ልክ እናስገባቸዋለን” ጊዜ ያለፈበት የፉከራ ቃል             

Kiyyaa Suuraa Kiyyaa Gonfaa

ከሰሞኑ አቶ አባይ ፀሃዬ አዲሱን የፊንፊኔ ማስተር ፕላን አስመልክተው የተናገሩት የዛቻና የፉከራ ቃል መላውን የኦሮሞ ህዝብ ያስቆጣና ምናልባትም አዲሱ የማስተር ፕላን ፕሮግራም በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ፍፁም ተቀባይነት የሌለው እና ከባድ መስዋትነት የተከፈለበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የአቶ አባይ ፀሃዬ  “ልክ ይገባሉ” የሚለው ያረጀና ጊዜው ያለፈበት የፉከራ ቃል የኦሮሞን ህዝብ በበለጠ ለነፃነቱ የሚያደርገውን ትግል አጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያነሳሳ ንቀት የተሞላበት ንግግር ነው::

እንዲህ ያለው ዛቻና ማስፈራሪያ ለዘመናት የተጨቆነንና የነፃነት ጥያቄን አንግቦ የተነሳን ሰፊ ህዝብ በይበልጥ እንዲጠናከርና የተፈረደበትን የልክ ይገባል ዛቻ አፀፋዊ ምላሽ ለመስጠት እራሱን ዝግጁ እንዲያደርግ የሚጋብዝ ባለንበት ዘመን ሊሰነዘር የማይገባ አፀያፊ ቃል ነው:: ተናጋሪው የወቅቱ ባለስልጣን በተለይ በኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳድር በየደረጃው የሚገኙ ባለስልጣናትን ለአዲሱ የፊንፊኔ ማስተር ፕላን ፕሮግራም ተፈፃሚነት ግንባር ቀደም እንቅፋቶች መሆናቸውን ንቀት በተሞላበት መልኩ ከተናገሩ በኋላ እንደርሳቸው “የልክ ይገባል” ፉከራ ከሆነ እነዚህ በማስተር ፕላኑ ላይ ተቃውሞ ያላቸውና እንቅፋት የሆኑ በየደረጃው ያሉ የክልሉ ሰራተኞች የመጀመሪያ ልክ የሚገቡ ሰዎች ይሆናሉ::

ከኚሁ የዘመናችን ባለስልጣን የማስፈራሪያ ንግግር አንድ ልብ ብለን መገንዘብ ያለብን ነገር ያለ ይመስለኛል ይሔውም ለልማት ሳይሆን ለጥፋት ቆርጠው የተነሱ የህወሃት አባላት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስ በከፍተኛ ስልጣን ከሚገኙ የክልሉ ተወላጆች እስከ ወረዳ ቀበሌ በሚገኙ የኦሮሞ ተወላጆች ያልጠበቁትን ከፍተኛ ተቃውሞ የተመለከቱበት ወቅት ከመሆኑ አንፃር ምናልባት ቀድሞ የታየው ተቃውሞ መልኩን ቀይሮ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል ይችላል የሚል ስጋት ስለሚፈጠር እንደ አማራጭ ሊጠቀሙ የሚችሉበት ነገር በግለሰብም ደረጃ ሆነ ባጠቃላይ እንደ ህዝብ የማስፈራሪያና የማሸማቀቂያ ቃላትን በመወርወር ከወዲሁ የተቃውሞ ድምፆችን ለማቀጨጭ መሞከር ነው:: አቶ አባይ ፀሃዬ የፈፀሙትም ይሄንኑ ይመስለኛል::

ያለንበት ዘመን አንዱ ሌላውን ልክ እያስገባ የሚኖርበት ዘመን አይደለም:: ይልቁኑ የመብት ጥያቄ ለሚያነሳ ህዝብ ተገቢውን መልስ በመስጠት በሃገሪቱ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠርና የህዝቦች መብት በእኩል አይን ሊከበር የሚችልበትን መንገድ መቀየስ እንጂ::  አቶ አባይ ፀሃዬ ይህ የገባቸው አይመስሉም:: ለ24 ዓመታት በህዝብ ጫንቃ ላይ ቁጭ ብሎ ህዝብን በንቀት አይን ሲመለከቱበት የነበረ ጊዜ አሁን ያበቃለት መሆኑን መረዳት ይኖርባቸዋል:: ብሶት ህውሃትን ብቻ ሳይሆን ሌላውንም የማይወልድበት ምክንያት ሊኖር አይችልምና::

6 thoughts on ““ልክ እናስገባቸዋለን” ጊዜ ያለፈበት የፉከራ ቃል

  1. Oromoon yomiyyuu caalaa amma tokkummaa isaa cimsatee waraanaa isarratti banameef deebii yoo keenuu baatee Abaay tsahaaye mitti tigreen nucina jirtuu tokkoon tokkoon ishee nuratti fincaa`uun ishee hinafuu.OPDO`n illee muranoo isheen agarsiistee kan nama kakaasuu fii haarka wal qabanee tigree of irraa akka darbiinuu haamileenuuf tahaa jirtii.afaan tokkoo haasofnaa hojiin keenyaas tokkoo haata`uu.
    Bilisummaa Ummata Oromoof!!!

  2. TPLF በኦሮሞ ህዝብ ላይ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በኢትዮዽያ ህዝብ ላይ ዛቻ የጀመሩት ዛሬ አይደለም:: የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊም እንዲሁ ሲደነፋ ዓለም በቃኝ ብሎ ኮበለለ:: የዚህኛው ደሞ እጅግ የሚገርም ነው:: ድርቅ ያለ ዛቻ:: የዚህ አይነቱን ልቡ ያበጠ ሰው ዛቻ እንዲሁ social media ላይ በመጮህ ብቻ ልናረግበው አንችልም አሁን ሃይላችንን ማጠናከር ያለብን ወሳኝ ሰዓት ላይ ነን:: የዚህ ሰውዬ ድንፋታ ወያኔ ምን ያህል እድሜው አጭር እንደሆነ የሚያመላክት ነው::

  3. Sareen kuun, qeerroon caliisee laalaa isa fakkaatee,haanga lubbuun nama tokkoo haafutti wareegama barbaachisuu kafaluu qabnaa.haadhuftuu tokkoon tokkoon ishee lafuuma Oromiyyaa irratti awwaallaa.

  4. Wara ODF maaliif caliisan? haasaa tigrichaa isaan hin ilaalatuu? moo yoo deebii keenan kaayyoo gara Ethiopia galuudhaa jeedhan guufu nuratti tahaa jeedhani yaadan laataa?anii personaly baayyeen gadee.namnii kamiiyuu ilaalchii issaa addaa addaa.ilaalchaan walii qoqqoodamuu ni danda`aama.garuu gaafii enyuumaa irratti hundii keenyaayyu tokkoo ta`uu qabnaa tuure.ummata Oromoof qabsoofnaa nuun jeechaa jiruu garuu ummata Oromoo irratti waraanii yeroo banamuu mana cuufatanii ta`aanii dhaga`uun of goowomsuu dha.yaa jarana qabsoon deemaa jirtuu wayyaanee waliin qoofa osso hin tahiin qooree marqaa keessaa tahaanii kan nuwaraanaa jiran waliinis tahuu qabaa.period.

  5. Tokkuummaa keenyaa yoo ciimsinee malle jarii kuun waan dubbatee raawwachuuf dubbati waan jeetu natti hin fakkaatuu.nutti addaan qoqqodamuun keenyaa isaaniif toolera.ummata dhiga namaa dheboote dha warii TPLF hundiinuu.obboollewwan keenyaa AMBO irratti ficiisiisnee,ammas taanaan qeerroo keenyaa teenyee ficiisiisu malle jijjiramnii dhufuu waan jiruu natti hin fakkaatuu.diina ofii irraa itiisuuf mee bakka tokkoo dhufnee kaayyoo nutti dhaabbaneef yaa hojjanuu.akka ilaalcha kotiitti kan duursu kana natti fakkaataa.
    Injjiffannoon ummata Oromoof haata`uu.

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s